አርኪቭ

 

Torsdag 23. november  2006

ጥምቀተ እግዚእ ኢየሱስ ልደተ እግዚእ ኢየሱስ

 

 

 

-

 

ምልክት ነው።

 

ቤተክርስቲያን ሁሉንም ያለ ምሳሌና ያለ ትርጉም የምትፈጽመው የላትም ። እኛም ስለበዓሉ

ትርጓሜ ካወቅን ጌታ በተናቀችው አህያ ከብሮ እንደዋለ በዚህ ዓለም አልባሌና ተርታ መስለው

ለፈጣሪያቸው በትህትና በመገዛት ከሰብአው ዓለም በጾም በጸሎት በትሩፋት ተለይተው ዓለም

እንደ ኋላ ቀርና እንደ አላዋቂ የቆጠረቻቸውን ክርስቲያኖች ላይ ጌታ ከብሮ ገኖ ለመታየቱ ምሳሌ

ስለሆነ እንደ አህያይቱ በልቦናችን ዙፋን ላይ ነግሶ እንዲኖር ልባችንን ክፍት እናድርግ!!

        በዓሉን በዓለ ጥዒና ያድርግልን ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

 

Text Box: 	
		
		

		

	
		
		”የታሰሩትን አህዮች ፈታችሁ አምጡልኝ!” ማቴ 21፡2 
	
	ሕዝበ ክርስቲያን እንኳን ለበዓለ ሆሣዕና አደረሳችሁ!
	
	ሆሣዕና ማለት መድሃኒት ማለት ነው። በተብራራ ትርጉሙ ሲታይ ሆሣዕና ማለት ’አሁን አድን’ ማለት ሲሆን ’ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት፤ ብሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር’ እያሉ በእለቱ ፈጣሪያቸውን በደስታ ዝማሬ እየዘለሉ ሲያመሰግኑ የነበሩትን የህፃናቱንና የአዕሩጋን ድምጽ የምናስብበት ዕለት ነው።
	ይህ በታላቁ አብይ ጾም መገባደጃ ላይ በስምንተኛው እሑድ የሚውለው ቀን ጌታ በትንቢት እንደተነገረለት በአህያይቱና በውርንጫዋ ለይ ተቀምጦ መላዋ ኢየሩሳሌም እስክትንቀጠቀጥ ድረስ በታላቅ ሞገስ ከብሮ ወደ ቤተ መቅደስ በዑደት የገባበት የክብረ በዓሉ ቀን ሲሆን በዕለቱ ’ማንም ቢጠይቃችሁ ለጌታ ያስፈልገዋል በሉ’ ተብሎ በተነገረው መሰረት ተፈትተው ከመጡት አህዮች ጀምሮ እስከ ቤተ_መቅደስ ያደረገው ጉዞ ሁሉ ታላቅ መንፈሳዊ ምስጢራት የተፈፀሙበት መሆኑን ልናስተውለው ይገባል።
	ትርጓሜው 
1.ሁለቱ አህዮች የአዳምና የሔዋን ምሳሌ ሲሆን መታሰራቸው አዳምና ሔዋን ዕፀ በለስ በልተው በግብርናተአስረው  ዲያቢሎስ በሲኦል ቁራኛ ታስረው ለመኖራቸው ምሳሌ መፈታታቸው ጌታችን ሰው ሆኖ ደሙን አፍስሶ ነፃ ለማውጣቱ

2.ሁለቱ አህዮች የብሉይና የሐዲስ ምሳሌ ሲሆኑ በማቴ 21  ከቁጥር 1 እስከ ፍጻሜ እንደ ተጠቀሰው በአህያይቱ እስከ ቤተ መቅደስ በውርንጫዋ ደግሞ በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ዑደት አድርጓል። ይህም ሕገ ኦሪት( ብሉይ) ስትመራን ኖራ በአዲሱ ህግ  (በሐዲስ ኪዳን) ለመተካቷ ምሳሌ ነው።

 3.የዘንባባ ዝንጣፊ _ቀደም ሲል በዘመነ ኖህ ርግብ ማየ አይህ ለመድረቁ የብስራት ምልክት አምጥታለች። በመጽሐፈ ዮዲትም እንደምንረዳው ዮዲት የአህዛብ ንጉስ ሆሊሆርኒስን ድል ነስታ ስትመጣ ህዝቡ የዘንባባ ዝንጣፊ ይዞ በሆታ ተቀብሏታል። መጽ (ዮዲትን ተመልከት) ስለዚህ ማየ ኃጢያት ቁሞ ማየ ሕይወት እንደተሰጠን ግብርናተ ዲያቢሎስ ቀርቶልን ግብርናተ ሥላሴን መታተማችንን ለማብሰር ምልክት ሲሆን ዲያቢሎስ የመሸነፉ ጌታ ድል የማድረጉ የድል ምልክት ነው።

ቤተክርስቲያን ሁሉንም ያለ ምሳሌና ያለ ትርጉም የምትፈጽመው የላትም ። እኛም ስለበዓሉ
ትርጓሜ ካወቅን ጌታ በተናቀችው አህያ ከብሮ እንደዋለ በዚህ ዓለም አልባሌና ተርታ መስለው
ለፈጣሪያቸው በትህትና በመገዛት ከሰብአው ዓለም በጾም በጸሎት በትሩፋት ተለይተው ዓለም
እንደ ኋላ ቀርና እንደ አላዋቂ የቆጠረቻቸውን ክርስቲያኖች ላይ ጌታ ከብሮ ገኖ ለመታየቱ ምሳሌ
ስለሆነ እንደ አህያይቱ በልቦናችን ዙፋን ላይ ነግሶ እንዲኖር ልባችንን ክፍት እናድርግ!!
		በዓሉን በዓለ ጥዒና ያድርግልን ወስብሐት ለእግዚአብሔር። 
፡                   ሆሣዕና